የአቦል ቲቪ ተመልካቾችን ወደ ኢትዮጵያ ውብ መልክዓ ምድሮችና ድንቅ ባህሎች የሚወስደው አዲስ የጉዞ ሪያሊቲ ሾው "Out And About" በዚህ ሳምንት ጀምሯል። ይህ ፕሮግራም የሀገሪቱን ታሪክ፣ አኗኗር ዘይቤ፣ መዝናኛዎች እና እና የጉዞ ገጠመኞችን በአዲስ መነጽር ያሳያል።
በ "Out And About" ምን ይጠብቀናል?
Out And About ምዕራፍ አንድ ተመልካቾችን ከታላላቅ ታሪካዊ ስፍራዎች እስከ አዳዲስ መዝናኛአዎች ድረስ አብሮ ይወስዳል።
የሾዉ አቅራቢ ኪም በጉዞዋ፡
- የኢትዮጵያን ታሪካዊ ቅርሶች እና ዓለም አቀፍ እውቅና ያገኙ ባህላዊ በዓላትን ትጎበኛለች
- በአስደናቂ የእግር ጉዞዎች እና ልዩ የመዝናኛዎች ላይ ትሳተፋለች
- እንደ ጎልፍ፣ የፈረስ ግልቢያ እና የሞተር ስፖርት ውድድሮች ካሉ ዘመናዊ የከተማ ስፖርታዊ ክንውኖች ጋር ተመልካቾችን ታስተዋውቃለች
- የወጣቶች ማህበራዊ እንቅስቃሴዎች እና አዳዲስ የከተማ ለውጦችን ትቃኛለች
በአጠቃላይ፣ ይህ ሾው የኢትዮጵያን ባህል፣ አኗኗር እና ጉልህ ልምዶች በማክበር የተሞላ ድንቅ ጉዞ ነው።
አስጎብኚያችን፡ ኪም - ኮሪያዊቷ ሐበሻ
የዚህ አስደሳች ጉዞ አቅራቢ ኪም፣ በራሷ ልዩ ማንነትና የሙያ ብቃት ትታወቃለች። ኮሪያዊት ሐበሻ የሆነችው ኪም፣ ተሰጥኦዋ በቴሌቪዥን አቅራቢነት፣ በሞዴሊንግ፣ በዝግጅት አደራጅነት እና እንደ ሜካፕ ባሉ ጥበባት ውስጥ የሚንፀባረቅ ሁለገብ ወጣት ናት።
በጉጉትና በፍቅር የምትመራው ኪም፣ አዳዲስ አካባቢዎችን መጎብኘት፣ ከተለያዩ ሰዎች ጋር መገናኘት እና አዳዲስ የምግብ ተሞክሮዎች ላይ መሳተፍ ደስታ ይሰጡዋታል። ለሙዚቃና ለጉብኝት ላይ ያላት ጥልቅ ፍቅር፣ እንዲሁም የምታንፀባርቀው ተፈጥሯዊ ወኔና ስብዕና፣ ከማንኛውም ሰው ጋር ከመግባባት ተፈጥሯዊ ችሎታዋ ጋር ተዳምሮ፣ Out And Aboutን ለመምራት ፍጹም ተመራጭ ያደርጋታል!
እናንተም ይህን አስደናቂ ጉዞ እንድትከተሉ ተጋብዛችኋል!
Out And About ዘወትር ዕረቡ ከምሽቱ 2፡00 በአቦል ቲቪ እንዳያመልጥዎ!
የአቦል መዝናኛዎችን ለመከታተል ደምበኝነትዎን ያስቀጥሉ፡ https://mydstv-thiane.onelink.me/ivCe/qpuy2sa6
