Logo

ስለ ሰርካለም ጌታነህ በአርብ ምሽት ፌስቡክ ላይቭ ላይ የተረዳናቸው ነገሮች

ዜና
02 ጁላይ 2021
የአደይ ተዋናይ ሰርካለም ጌታነህ ፌስቡክ ላይቭ ላይ ትቀርባለች።

በተወዳጁ የአቦል ቲቪ ድራማ ላይ ወይዘሮ ሮማንን ሆና የምትተውነው ሰርካለም ጌታነህ ባለፈው አርብ ምሽት ከድራማው አድናቂዎች ጋር በፌስቡክ ላይቭ ቆይታ አድርጋለች፡፡ ምሽቱን ያሳለፈችው በአቦል ቲቪ ማህበራዊ ሚዲያ ስለ አደይ ድራማ እና ስለ ወይዘሮ ሮማን የቀረቡትን ጥያቄዎች ለተመልካቾች በመመለስ ነው። በዚህ ጊዜ ስለ ተዋናይቷ ማንነት አዲስና አስደናቂ ነገሮችን ተምረናል።

እነዚህ ከሰርካለም ጌታነህ ባደረግናቸው የፌስቡክ ላይቭ ቆይታ ላይ የሰማናቸው ነገሮች ናቸው፡

  1. በልጅነቷ የጤና ባለሞያ ነበረች

በአደይ ላይ ወይዘሮ ሮማንን ሆና ስትቀርብ በመላ ታዳሚዎች ተደንቃ ስለነበር ከዚህ በፊት በትወና ሞያ ውስጥ ብዙ ጊዜ አሳልፋለች ብሎ ማሰብ ይቻላል፣ በፌስቡክ ላይቭ ላይ ግን ሰርካለም ህይወቷን ያሳለፈችው በጤና ባለሞያነት እንደሆነ ተረድተናል። ይሄ በአደይ ድራማ ላይ ያቀረበችውን ችሎታ ይበልጥ አስገራሚ አድርጎታል።

  1. ቲያትሪካል አርት በምትማርበት ጊዜ ላይ ብዙ እንቅፋቶች ገጥመዋት ነበር

ወደ ቲያትሪካል አርት ትምህርት ቤት ለምዝገባ ስትሄድ መኪና አደጋ ደርሶባት ነበር፤ ግን ይሄ እንቅፋት ተስፋ ሳያስቆርጣት ትምህርቱን መቀጠል ችላለች። በሚያሳዝን ሁኔታ ሌላ የመኪና አደጋ በትምህርቱ ሁለተኛ አመት ላይ እያለች ደርሶባት ነበር፤ ግን ይህ አጋጣሚ ሳያስቆማት ትምህርቷን በመቀጠሏ ተወዳጇ የአደይ ድራማ ገጸ ባህሪ ወይዘሮ ሮማንን ማቅረብ ችላለች።

  1. ለአደይ ድራማ ዳይሬክተር ሰውመሆን እና ዲዛይነር ዳግማዊት ታላቅ አድናቆት አላት

በአደይ ድራማ ላይ የሚቀርቡት እጅግ በጣም ተወዳጅ ገጸ ባህሪዎች መገንባት እንዲቻል ዳይሬክተር ሰውመሆን ለሚሰራው ስራ አድናቆቷን አሳውቃለች። ድራማ ውስጥ የቀረቡት የሚያስደንቁ ዲዛይኖችን ላቀረበችው ዳግማዊት ምስጋና እና አድንቆቷን አቅርባለች። በድራማ ውስጥ እንደቤተሰብ ሆነው መስራት በመቻላቸው እና በመተባበራቸው ተዋንያን እና ክሩውን አመስግናለች።

ከፌስቡክ ላይቩ ላይ በጣም የወደዱት ምን ነበር? አስተያየትዎን ያሳውቁን!

አደይ ድራማ ምዕራፍ 2 ሰኔ 21 ጀምሯል። ከሰኞ እስከ አርብ በአቦል ቲቪ፣ ዲኤስቲቪ ቻናል 146 ከምሽቱ 2፡00 ይከታተሉ!